- 12Jun
ቅድስት ስላሴ (A-OT-Trinity)
1ኛ ንባብ፥ ዘጸአት 34፥4-6.8-9 √ “እግዚአብሔር በደመና ወርዶ ከሙሴ ጋር በዚያ ቆመ” (ኦሪት ዘጸአት 34፥5)። እግዚአብሔር በደመና ምስል ይገለጻል። ደመና ግን ጭጋግና ጨለማ ነው፥ ምንም ነገር ማየት አይቻልም። በጭጋግ ውስጥ ግን ምንም ባይታይም፣ ሰው በውስጡ እየኖረ አለማየትን ይለምዳል። ዋናው ነገር ማየት አይደለም፣ አለማየትን መልመድ ነው እንጂ። √ እግዚአብሔር በደመና ምስል ውስጥ ይገለጻል፣ ደመና የመለኮታዊ ጭጋግ ምስል ነው፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር የማይመረመር አምላክ እና የማይታወቅ ምስጢር ነው። በሚገለጽበት ጊዜ በደመና ተደብቆ ምስጢር መሆኑን አይተውም። ይልቁንም ነፍሳችንን በምስጢሩ ያሳትፋል። > እኛ በደመና ውስጥ አናይም እንጂ በደመና ውስጥ እንደገባን እናውቃለን። እግዚአብሔር አይታይም እንጂ ወደ እርሱ ስንቀርብ በመለኮታዊ ደመና እንደገባን እንገነዘባለን። ነገር ግን እግዚአብሔር በሚገለጽበት ጊዜ ምስጢሩን አያስወግድም እንጂ በምስጢሩ ያሳትፈናል። ደመና እግዚአብሔር ምስጢሩን ሳይተው በምስጢሩ እንደሚያሳትፈን የሚገልጽ ምስል ነው። እግዚአብሔር ከእኛ በላይ ነው፥ በእርሱ…
10JunSolemnity of the Body and Blood of Christ
√ The whole in one fragment. The solemnity of the Body and Blood of Christ is the solemnity of the whole in a fragment. Because everything is in a fragment. A particle is enough for everything to be there. > If everything is in a fragment, we will not struggle to take anything away. If we were to keep all the things that existed before us and that will exist after us, we wouldn’t be able to do it. But if everything is in a fragment, we can keep everything in one. > It is the solemnity of the Body and Blood of Christ. But is Christ alive or dead? Alive. And is his Body alive or dead? Alive (if…
05Junየጳራቅሊጦስ (A-PHASIKA-Pentecost)
1ኛ ንባብ፥ የሐዋርያት ሥራ፥ 2,1-11 √ ነፋስ የሚመስለው ድምጽ ቤቱን ሞላው። እሳት ወርዶ በእያንዳንዳቸው ላይ አረፈ። ደቀመዛሙርቱም ወደ አደባባይ ወጥተው በተለያዩ ቋንቋዎች የእግዚአብሔርን ቃል መናገር ጀመሩ። √ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ቃል ከመፅነስ በቀር ምንም ሌላ ተልእኮ የለውም። መንፈስ ቅዱስ ልክ በድንግል ማርያም ማህፀን ውስጥ ቃሉን በመፅነስ ልጅ እንድትወልድ እንዳስቻላት፣ አሁንም በሐዋርያት ላይ ራሱን በማፍሰስ በልባቸው ውስጥ ክርስቶስን እንዲፀንሱ፣ በሥራቸውም እርሱን እንዲያፈሩና ለአለም ሁሉ እርሱን እንዲያበስሩም ያስችላቸዋል። “ዝግ በነበረ በላይኛው ክፍል በኩል የገባ መንፈስ፣ ኢየሱስ በተፀነሰበት ጊዜም ዝግ በነበረ በድንግል ማህፀን በኩል የገባ መንፈስ ራሱ ነው” (Gregory the Great †604) የክርስትና ታሪክ እና የዘመናት ይዘት በትክክል የዚህ መለኮታዊ ፅንስና ልደት ማራዘሚያ ነው። የማርያም ሕይወት ፍሬ የኢየሱስ ልደት ነው። አጠቃላይ የቤተክርስቲያን ታሪክ ፍሬ እስከ ዓለም ዳርቻ የሚደርስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን የክርስቶስ ፍጻሜ…
30Mayየኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት (A-PHASIKA-Ascension)
1ኛ ንባብ፥ የሐዋርያት ሥራ 1,1-11 √ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ኢየሱስ ከደቀመዛሙርቱ አይን ተለይቶ ቀረ። እስከዚያ ቀን ድረስ እየሱስ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ይኖርና ይበላ ነበር፤ በገሊላ መንገዶች ላይም ከእነርሱ ጋር ይራመድ ነበር፣ ድምጹን ለመስማት እና ተዓምርን ለማግኘት ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ይሰባሰቡ ነበር። አሁን ግን ከእነርሱ ተለይቶ ቀርቷል። ነገር ግን እየሱስ ደቀመዛሙርቱን አልተወም፣ ይልቁን በውስጣቸው መኖር ጀምሯል። ካረገ በኋላ እየሱስ ከአይናቸው ቢለይም በነፍሳቸው ውስጥ መኖር ጀምሯል። በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ክርስቶስ በደቀመዛምርቱ ይኖራልና ደቀመዛሙርቱም በእርሱ ይኖራሉ። “በእኔ ኑሩ፣ እኔም በእናንተ እኖራለሁ” የሚል የኢየሱስ ቃል እና ትእዛዝ እንደሁ ተፈጽሟል (ዮሐንስ 15፥4)። √ ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስን ሲያናግሩ ለመጀመርያ ጊዜ “ጌታ ሆይ!” ብለው ይጠሩታል (6)። ‘ጌታ’ በግሪክ ቋንቋ ‘ኪርዮስ’ (κύριος) ይባላል። ‘ኪርዮስ’ ማለት ደግሞ በሲና ተራራ ላይ እግዚአብሐር ለሙሴ የገለጸለት ስም ነው። ይህ ስም በብሉይ ኪዳን ማንበብ የተከለከለ ስለነበረ፣…
16Mayየፋሲካ 5ኛ እሁድ (A-PHASIKA-5)
ወንገል፥ ዮሐንስ 14,1-12 √ መንገድና እውነት ሕይወትም እኔ ነኝ (6)፣ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ማንም ወደ አብ የሚመጣ የለም፥ ኢየሱስ ወደ አብ የሚመራ መንገድ ነው። ወደ ሰማይ መድረስ የምንችል፥ > ትእዛዞቹን በመፈጸም > በእምነት አማካይነት፣ ምክንያቱም ጌታችን የመጣ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለምን ሕይወት እንዲያገኝ ነው” (ዮሐንስ 3,15) > የእርሱን ምሳሌ በመከተል፣ ምክንያቱም ክርስቶስን ካልመሰለ ማንም ወደ አብ የሚመጣ የለም > ከሁሉ በላይ፣ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ በመስቀል ላይ ስለሞተ > ክርስቶስ ከእርሱ ጋር አንድ ተፈጥሮ ያለውን አባቱ ስለገለጸ። √ ኢየሱስ መንገድ ነው። እርሱ ሰማይና ምድርን የሚያገናኝ ብቸኛው መንገድ ነው። በመካከላችን በኖረበት ጊዜ በዚህ ምድር ላይ የእርምጃዎቹን ግልጽ ዱካዎች ትቶአል። የእርሱ እርምጃዎች የዘመናት ብልሽትና የጠላት ሸፍጥ ማጥፋት ያልቻሉ የማይሰረዙ እርምጃዎች ናቸው። “መንገድ የሆነው የሰው ፋና ወደሌለው ቆሻሻ አይመራንም። እውነት የሆነው በሐሰት አያፌዝብንም። ሕይወት የሆነው…
15May[LR2] About Bill Gates
Bill Gates ለአለም ጤና ድርጅት (WHO) ቀዳሚ የገንዘብ ምንጭ ነው። ቀደም ብሎ በ 2018 ከዳቮስ ጓደኞቹ ጋር ተሰማምቶ ወረርሽኝ እንደሚከሰት ትንቢት ተንብዮ ነበረ። ለረጅም አመታት ህዝብን በማጥፋት በአለም ላይ የቁጥጥር እቅዶችን ሲያበረታታ መቆየቱ ይታወቃል። “በአዳዲስ ክትባቶች አማካይነትና በስነ ተዋልዶ ጤና ላይ ጥሩ ሥራ ከሠራን፣ የአለምን ህዝብ በ 10-15% መቀነስ እንችላለን” (B.G.) “አለምን ማዳን የሚቻለው የሰው ዘር በማጥፋት ዘመቻ ብቻ ነው (genocide)” (B.G.) በክትባቶቹ ምክንያት በአፍሪካ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች መካን ሆነዋል። በክትባቶቹ ምክንያት ሕንድ ውስጥ 500,000 ሕፃናትን ሽባ ያደረገ የፖሊዮ ወረርሽኝ ተከስቷል። በአፍሪካ ውስጥ የአለም ጤና ድርጅትና Bill Gates ‘የለገሱት’ DPT ክትባቶች የሕጻናትን ህይወት ቀጥፏል፤ በMonsanto ታቅደው በBill Gates ‘የተለገሱት’ ምግቦች፣ ሕዝብን በሙሉ መካን የሚያደርጉ ናቸው። ለኮሮና ቫይሩስ ክትባት አያስፈልግም፥ sero-therapy ቀደም ብሎ 100% ታካሚዎችን እየፈወሰ ነው። ወጪ ስለሌለው ግን…
09Mayየፋሲካ 4ኛ እሁድ (A-Phasika-4)
ወንገል፥ ዮሐንስ 10፥1-10 √ ወደ በጎች በረት በበር የማይገባ ሰው ሌባና ዘራፊ ነው (1)፥ መንጋውን ቀስ ብሎና በድብቅ መጉዳት ይቻላል፣ ወይም በግልጽና ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም መጉዳት ይቻላል። የክርስቶስ ጠላቶች በሁለቱም ዘዴዎች ተጠቅመው ያውቃሉ። “ውጭ ስንት በጎች አሉ፣ ውስጥ ስንት ተኩላዎች አሉ? ውስጥ ስንት በጎች አሉ፣ ውጭ ስንት ተኩላዎች አሉ?” (Augustine of Hippo †430) √ እረኛ የራሱን በጎች በየስማቸው ይጠራቸዋል (3)፣ በጎቹም ድምጹን ስለሚያውቁ ይከተሉታል (3-5)፥ ምሽት ላይ ብዙ መንጋዎች በዘበኛ እየተጠበቁ ሌሊቱን በሙሉ ያድሩበት በነበረ በአንድ በረት ውስጥ ይሰበሰቡ ነበር። በማለዳ እያንዳንዱ እረኛ ወደ አጥሩ በር መጥቶ በጎቹን አንድ ላይ ይጠራል። በጎቹ ተሰብስበው በረቱን ትተው እረኛውን ይከተላሉ። በጎቹ እንዳይጠፉ ደጋግሞ እረኛው ድምፁን እያሰማ እነሱን ወደ መስክ ስፍራ ለመምራት ከፊት ለፊታቸው ይጓዝ ነበር። መለኮታዊ ትምህርት ለመግለጽ ጌታችን ኢየሱስ ለአድማጮቹ በጣም የታወቀ የነበረውን ይህ…
02Mayየፋሲካ 3ኛ እሁድ (A PHASIKA-3)
ወንገል፥ ሉቃስ 24፥13-35 √ ሁለት ደቀመዛሙርት (13)፥ አንዱ ቀለዮጳ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ አይታወቅም፣ በስሙ ፋንታ የእያንዳንዳችንን ስም መወከል እንችላለን። ሁለቱ ደቀመዛሙርት ይጓዙ ነበር፥ ሰው በምኞቱ ተመርቶ ሁል ጊዜ መንገደኛ ነው። እየተጓዙ እርስ በእርሳቸወ ይወያዩ ነበር (14)፥ እኛ የምንወያይ በልባችን ስላለው የምንመኘውና የምንወደው ነገር ነው። √ ኢየሱስ ራሱ ወደ እነርሱ ይቀርባል (14)፥ ከሞት የተነሣ ክርስቶስ ወገኖቹን አይተውም፣ አሁን ለሁሉም ሰው እና በሁሉም ቦታ ለእነርሱ ቅርብ መሆን ይችላል። እንዲሁም በተዘጉ በሮች፣ በተሰወሩ አይኖች እና በደነደኑ ልቦች መግባት ይችላል። ወንጀለኛውን እስከ መስቀል ድረስ እንደፈለገ፣ አሁንም መንግሥቱን ይሰጠን ዘንድ እያንዳንዳችንን ይፈልጋል። √ ኢየሱስ በቅዱሳት መጽሐፍት ሁሉ ስለ እርሱ የተነገረውን እየጠቀሰ ያስረዳቸው ነበር (27)፥ ቅዱሳት መጻሕፍት አንድ መጽሐፍ ብቻ ናቸው እናም ይህ መጽሐፍ ራሱ ነው፣ ምክንያቱም ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ስለ ክርስቶስ ይናገራሉና በእርሱ ፍፃሜን ያገኛሉ። √ ከእነርሱ እንዳይለይ አጥብቀው…
17Apr[WW3] የመስቀል ርዕስ (Titulus Crucis)
“ጲላጦስ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ የሚል ጽሑፍ ጽፎ በመስቀሉ ራስጌ ላይ አኖረው። ኢየሱስ የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ስለነበረ፣ ከአይሁድ ብዙዎቹ ጽሑፉን አነበቡት፤ ጽሑፉም የተጻፈው በዕብራይስጥ በላቲንና በግሪክ ቋንቋ ነበረ” (ዮሐንስ 19፥19-20) ⇒ ወንጌላዊው ዮሐንስ በመስቀሉ ላይ የተጻፈው ጽሑፍ በዕብራይስጥ፣ በላቲንና በግሪክ ቋንቋ መሆኑን ሊነግረን ለምን ፈለገ? ለዚህ መልስ ለመስጠት፣ በመጀመሪያ በብሉይ ኪዳን ጊዜ በእግዚአብሔር ስም ዙሪያ የነበረ የቅድስናን ግንዛቤ መመልከት ያስፈልጋል። በኦሪት ዘጸአት መጽሐፍ ውስጥ እንደሚነበብ፣ በሲና ተራራ ላይ ራሱን በገለጸበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር ህዝቡን ከግብጻዊያን ቀንበር ነፃ እንዲያወጣ ሙሴን አዘዘ። በዚህ ታላቅ ትእዛዝ ፊት፣ ሙሴ ብዙ ጥያቄ ያቀርባል፥ ሕዝቡን እንዴት ያሳምናል? የእግዚአብሔር ስም ማን ነው? “እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው፥ ‘እኔ ያለሁና የምኖር ነኝ’፤ ስለዚህም ‘እኔ ነኝ ወደ እናንተ ልኮኛል’ በላቸው” (አሪት ዘጸአት 3፥14)። ትምህርተ ክርስቶስ እንደሚያስተምረው፣ ይህ ስም “እግዚአብሔር የሕላዊና…
16Aprፋሲካ፥ የነገሮችን ይዘት ለመገምገም እንማር (EASTER: seeing the essence of things)
የእግዚአብሔር ህግ ፍጹምነት በአሮጌው እና በአዲሱ መካከል ባለው አስደናቂ አንድነት ይገለጻል። በዘላለማዊ አምላክ ጥበበኛ እጅ (ማለትም በመንፈስ ቅዱስ) የሚደረግ ሁሉ በዋጋ የማይተመን ስፌት ይመስላል። ✓ ፋሲካ የሚለ ቃል ከዕብራይስጥ ‘ፐሳህ’ ከሚል ቃል የመጣ ነው። ትርጉሙም ‘ሽግግር’ ማለት ነው። ስለሆነም፥ ሁለቱም ክስተቶች በሽግግር ተለይተው ይታወቃሉ፥ 1. የአይሁድ ፋሲካ፣ ከአራት መቶ ዓመታት ስደት በኋላ ከግብጽ ባርነት ወደ ስጋዊ ነፃነት በሙሴ አማካይነት ተፈጽሞአል። 2. የክርስትና ፋሲካ፣ ከአዳም ኃጢአት በኋላ ከሰይጣን ባርነት ወደ መንፈሳዊ ነፃነት በክርስቶስ መሥዋዕት አማካይነት ተፈጽሞአል። ክርስቶስ የሰማይን በር ስለከፈተልን፥ እንደየትጋታችን ቢሆንም ወደ መጀመርያው ገነት መመለስ እንችላለን። ✓ አሁን የሁለቱን ተመሳሳይነት እንመልከት። የአይሁድ ሕግ በአይሁድ ፋሲካ ወይም በቂጣ በዓል ቀን ለመስዋእት ከቀረበ በግ ጋር፣ እርሾ ያልገባበት ቂጣ እና መራራ እፅዋት እንዲበላ ያዝዛል፥ 1. በግ የንጽህናና የየዋህነት ምልክት ነው፣ በዚህ ምክንያት በግ…

መግቢያ - Entrance
1 ነገሥት 17፡2-7 ያንብቡ፥ የእስራኤል ሕዝብ የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት ስላልፈለገ፣ እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያሰን ወደ በረሀ ሄዶ በምስጥራዊ ቦታ እንዲሸሸግ ነገረው። በዚህ ምክንያት ሁለት ተቃራኒ ሁኔታዎችን ማነፃፀር እንችላለን፥ በአንድ በኩል የእግዚአብሔርን ድምጽ ያጣው ሕዝብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ በከሪት ሽለቆ ከእግዚአብሔር ቀጥተኛ መመሪያ እና ምግብ የሚቀበል ነቢይ። ስለዚህ የእግዚአብሔር ድምፅ አሁንም ድረስ ወደሚሰማበት ምስጥራዊ ሸለቆ እንግባ።

የታችኛው ክፍል - Lower Room
በዚህ ክፍል ውስጥ ከማህበራዊ ጉዳይና ከዓለም አቀፍ መስተዳደር ጉዳዮች ጀምሬ በመጽሐፍ ቅዱስ እና በጥንታዊ የክርስቲያን ትምህርት በመሞርክስ፣ አንዳንድ ወሳኝ ግንዛቤዎች አቀርብላችኋለሁ። የሐዋርያውን ጳውሎስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ያንብቡ፥ “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ” (ወደ ሮሜ ሰዎች - ምዕራፍ 12፡2)።

የላይኛው ክፍል - Upper Room
አሁን ባለን ታሪክ ውስጥ ጣዕሙን እንዳጣ ጨው ሆነው የተወሰኑ ክርስቲያን አማኞች እና በተለይ መሪዎች የዚህን ዓለም አካሄድ ለመከተል ከፍተኛ ጉጉት ያድርባቸዋል። ለሰርዴስ መልአክ የተሰጠውን ምክር ያስታውሱ፥ “የነቃህ ሁን፣ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና” (የዮሐንስ ራእይ - ምዕራፍ 3፡2)። ክርስቶስ ቀርቦአል፣ ሲመጣም ከጓደኞቹ ቁጥር መገኘት እንፈልጋለን።

የውኃ ጉድጓድ - Water Well
ከጊዜ ወደ ጊዜ ፈጽሞ በማይደርቁ ጥንታዊ ምንጮች አጠገብ አርፌ ማታደስን አገኛለሁ። “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?” (መዝሙረ ዳዊት - ምዕራፍ 42)። ቀጣዮቹ ገጾች ክርስቶስን ለመማረክ ማንኛውንም ነገር ለመተው ከመረጡ ከዛሬና ትላንት አማኞች ልብ ይወጣሉ።

እንጀራ ቤት - Kitchen
እና እዚህ ደረስን። የክርስቶስ ወዳጅ ከምድራዊ ደስታ አይገለልም። “እግዚአብሔር ሥራህን ተቀብሎታልና ሂድ፥ እንጀራህን በደስታ ብላ፥ የወይን ጠጅህንም በተድላ ጠጣ” (መጽሐፈ መክብብ - ምዕራፍ 9፡7)። በእግዚአብሔር እይታ መሠረት የሚኖሩት ሰዎች የዝናን የወይን ጠጅ ይጠጣሉ፣ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ይሰማቸዋል።