- 20Mar
አድሜ ለአፍሪካ ተወካዮች፣ የተባበሩት መንግስታት ኮሚሽን ፅንስ ማስወረድና ሰዶማዊነትን የሚደግፈውን ውሳኔ ሊተው ነው
ሰዶማዊነትን የሚደግፈውን ውሳኔ ይጠበቅ ነበረ። ነገር ግን ባለፈው የካቲት መጨረሻ በተደመደመው የተባበሩት መንግስታት ማህበራዊ እድገት ኮሚሽን ፅንስ ስለ ማስወረድና ሰዶማዊነትን በተመለከተው ጉዳይ ምንም ፍንጭ እንኳን አልሰጠም። እንዲሆም የኮሚሽኑ የመጨረሻው ስምምነት “የወሲብና የስነ ተዋልዶ ጤና” የሚሉትን ቃላት ትቶ የቤተሰብን ብልጽግና የሚደግፉ መመሪያዎችን አካቶአል። በምላሽ የውርጃ ደጋፊ የሆነኑት የሜክሲኮ ተወካይ “ከመካከለኛ ዘመን ለመውጣት ያግዱናል” በማለት የአፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ ተወካዮችን ወቅሰዋል። እንደሚታወቀው በተባበሩት መንግስታት አነጋገር “የወሲብና የስነ ተዋልዶ ጤና” (sexual and reproductive health) ማለት ፅንስ ማስወገድን ማመቻቸት እንደ ማለት ነው። የአፍሪካ አገራት በመወከል የጂቡቲ ተወካይ “ቤተሰብ በማህበራዊ እድገት ውስጥ መሠረታዊ ሚና ይጫወታል፤ ቤተሰቦችን የሚደግፉት ፖሊሲዎች ማህበራዊ እኩልነትን ለማሳደግና ድህነትን ለማስወገድ ይረዳሉ” በማለት የኮሚሽን ስምምነት መልካም ገጽታዎችን ጎላ አድርገው ገልጸዋል። በቅርብ ዓመታት ውስጥም የተባበሩት መንግስታት ማህበራዊ እድገት ኮሚሽን “ብዙ አይነት ቤተሰብ አለ” በሚል አስተያየት…
20Marከየትኛው ፕላኔት?
እንደሚታወቀው፣ ቫቲካን እና የቻይና መንግስት የጋራ ትብብር ታሪካዊ ስምምነት ተፈራርመዋል። ነገር ግን የሆንግ ኮንግ (Hong Kong) ጳጳስ የነበሩ ካርዲናል ዘን (Zen) እንደሚሉት ከሆነ፣ ስምምነቱ ካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ለጠላቶችዋ አሳልፎ የሚሰጥ ነው። ለእውነተኛ እምነት ታማኝ ሆነው የቀሩት አማኞች በአባታቸው እጅ እንደተሰደዱ ይሰማቸዋል። የተፈረመው ስምምነት “እውነትን ይደብቃል፥ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ እና ቤኔዲክቶስ ሁልጊዜ እንዳስቀመጡት፣ እኛ አለን፣ እነርሱም አሉ፣ እኛና እነርሱ በፍጹም መስማማት አንችልም። እኛና እነርሱ የሚል ሁኔታ ያለፈ ታሪክ አይደለም፣ ዛሬም ያለ ታሪክ ነው። ይህን ሁኔታ ሊያጠፋ የሚችል አስማተኛ የለም። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ይህን በሚገባ ያውቃሉ። ካልሆነ እርሳቸው በሰዓታት ጸሎት ጠዋት ጠዋት የምናነበው “ሕዝቡን በምሕረት ስለ ጎበኘና ስላዳነ የእስራኤል አምላክ ጌታ ይመስገን… ከጠላቶቻችንና ከሚጠሉን እጅ አድኖናል” የሚሉትን የዘካርያስ ቃላት ማስወገድ ይኖርባቸዋል። ማታ ማታ የምናነበውም የማርያም መዝሙር እንዲህ ይላል፥ “በብርቱ ክንዱ ኃይሉን አሳይቶአል፤…
0 comments Read more