- 24Feb
“ህብስትና ወይን ጠጅ ከተቀደሱ በኋላ፣ እግዚአብሔር በመንግሥተሰማይ እንዳለ እዚህም ነው። ሰው ይህን ቢረዳ ኖሮ በፍቅር ይሞት ነበር” (Benedict XVI)
23Feb23Febዘወትር በስውር እንደተመኙት መልስ
“ሰዎች በቃላት ሊገለጽ በማይችል ብቸኝነት ውስጥ የሚኖሩ መሆናቸውን ይገነዘቡና የድህነታቸውን ፍርሃት ከተሰማቸው በኋላ፣ ልክ እንደ አዲስ ነገር ሆኖ ለክርስቶስ ታማኝ የሆነውን ያማኞች ታናሽ መንጋ ያገኛሉ፥ እርሱንም ዘወትር በልባቸው እንደተመኙት የውሃ ምንጭ የራሳቸውን ተስፋ አድርገው ያገኙታል” (Benedict XVI)
23Febየመንፈስ ኃይል
“ዛሬ ራስን መቻል ይባላል፣ በጥንት ዘመን የመንፈስ ኃይል ተብሎ ይጠራ ነበር፣ ፕላቶ መኖሪያዋ በሰው ልብ ውስጥ እንደነበረ ብሎ ፅፎአል፣ ልብ የስሜት ተምሳሌት ነው። ስሜት ግን ድክመት አይደለም፣ የነፍስ መጽናናትን የማያገኝ ሐዘንም አይደለም። ስሜት ድፍረት ነው። ስሜት ሁሉን ጥቅሞችና መሰናክሎች ካመዛዘንን በኋላ በእያንዳንዳችን ውሳኔ መነሻ ላይ የምናውቀው ድፍረት ነው። በጥቅም ወይም በድክመት ምክንያት የራሳችን ያልሆነ ውሳኔ ብናደርግ ግን ወዮልን! በራሳችን ሕይወት የውጭ ዜጋ ሆነን ከቀረን ወዮልን! ቤታችን! የመንፈስ ኃይል በራሳችን ቤት ውስጥ የውጭ ዜጋ ከመሆን ይጠብቀናል፣ ከራሳችን ጋር እና የቤታችን ነዋሪዎች መሆናችን እንዲሰማን ያደርጋል። ከራሳችን ጋር ተመሳሳይ የሚያደርገን የአእምሮ ጤንነት እዚህ አለ” (Romano Guardini 1885-1968)
23Feb“እኔ ክርስቲያን ነኝ። እንዲህ ብሎ የሚመልስ ሁሉንም ነገር በአንድ ጊዜ አውጃል፥ ሀገሩ ሙያው ቤተሰቡ። አማኝ የምድራዊ ከተማ ዜጋ ሳይሆን የሰማያዊ ኢየሩሳሌም ነዋሪ ነው” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
23Feb“ከመካከላችን አንድ አሥር ሰዎች ቅዱስ ሕይወት ብንመራ፣ ከተማውን ሁሉ የሚያበራ መብራት እናበራ ነበር” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
18Febየሃይማኖት ብዛት በእግዚአብሔር ፈቃድ (ሊቀ ጳጳሱ ፍራንሲስ)
“የሃይማኖቶች የከለር የፆታ የዘር እና የቋንቋ ብዛት በእግዚኣብሄር ጥበብ የተፈቀደ ሁኔታ ነው”። ይህ መግለጫ ባለፈው የካቲት 4 በአቡ ዳቢ (ኤሚሬትስ) ፍራንሲስ እና የአል-አህዛር ታላቁ ኢማም በፈራረሙት ስምምነት ላይ የሚገኝ ነው። በዘፍጥረት ምዕራፍ 11 የተጻፈው ግን እግዚአብሔር የቋንቋ መለያየትን እንደ ኃጢአት ቅጣት አድርጎ እንደፈቀደ ነው። ፍራንሲስ ሰዎችን እነደ መሥዋዕት የሚያርዱትን ሀይማኖቶች የእግዚአብሔር ፈቃድ አድርገው ይቆጥሯቸዋል ማለት ነው። ስላሴንና የክርስቶስን መለኮትነት የሚቃረኑትን እስልምና ወይም ይሁዲነት የእግዚአብሔር ፈቃድ አድርገው ይቆጥሯቸዋል። እግዚአብሔር እርስ በራሳቸው የሚቃረኑትን ሃይማኖቶች ከፈቀደ፣ የፍራንሲስ አምላክ ሁለት ተቃራኒ አስተያየት ይደግፋል ማለት ነው። ልክ እንደ ሰይጣን እውነትንና የእውነት ተቃራኒ ይፈልጋል፥ በእርግጥ ሰይጣን የውሸት መርህ ነው። ከኤሚሬትስ ሲመለሱ በበረራ ላይ በሚደረገው የጋዜጠኞች ጉባኤ ፍራንሲስ እንዲህ በማለት ተናግረዋል፥ “ከካቶሊክ አመለካከት አንፃር የፈረምነው ስምምነት ከሁለተኛ የቫቲካን ጉባኤ አንድ ሚሊሜትር እንኳን አልተንቀሳቀሰም። ይህ ሰነድ የተፈረመ በሁለተኛ…
18Febሁለት ቤተክርስቲያናት ሊኖሩ ይችላሉ
እኛ የዓመፅ ምሥጢር (2ኛ ወደ ተሰሎንቄ 2፡7) አሁንም በስራ ላይ እንደሆነ እናውቃለን፣ ነገር ግን የኃይሉን ሙሉ መጠን አናውቀውም። በእይታ ላይ ያለች ቤተክርስቲያን በጠላትዋ ድል ልትደረግ እንደምትችል አምኖ መቀበል ምንም ችግር የለውም፣ በዚህም ምክንያት ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ወደ ሌላ ቤተ ክርስቲያን መለወጥ እንደምትችል እናውቃለን። ሁለት ቤተክርስቲያናት ሊኖሩ ይችላሉ፥ አንደኛይቱ በይፋዊ እይታ ለይ ያለች፣ በአለም ሚድያ ፕሮፓጋንዳ በሐሰት ክብር የተጋነነች ቤተክርስቲያን ናት (ሌላው ቀርቶ አሻሚ የሆኑ አመለካከቶች ያሉት ጳጳስ ሊኖራት ይችላል)፤ ሌላዋ ደግሞ ለኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ የሆነ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ያላት፣ ከአንዳንድ ታማኝ ካህናትና አማኞች ጋር በምድር ዙሪያ እንደ ትንሽ መንጋ የተበታተነች፣ የዝምታ ቤተክርስቲያን ናት። ይህች ሁለተኛይቱ ቤተክርስቲያን የተስፋው ቃል የምትወርስ ነች፣ የመጀመርያ ግን ከሀዲ ናት። ሁለቱም ቤተክርስቲያናት በአንድ ጳጳስ ሊመሩ ስለሚችሉ አንድ አካል ይመስሉ ይሆናል። አሻሚ የሆኑ አመለካከቶች ያሉት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት…