- 17Apr
[WW3] የመስቀል ርዕስ (Titulus Crucis)
“ጲላጦስ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ የሚል ጽሑፍ ጽፎ በመስቀሉ ራስጌ ላይ አኖረው። ኢየሱስ የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ስለነበረ፣ ከአይሁድ ብዙዎቹ ጽሑፉን አነበቡት፤ ጽሑፉም የተጻፈው በዕብራይስጥ በላቲንና በግሪክ ቋንቋ ነበረ” (ዮሐንስ 19፥19-20) ⇒ ወንጌላዊው ዮሐንስ በመስቀሉ ላይ የተጻፈው ጽሑፍ በዕብራይስጥ፣ በላቲንና በግሪክ ቋንቋ መሆኑን ሊነግረን ለምን ፈለገ? ለዚህ መልስ ለመስጠት፣ በመጀመሪያ በብሉይ ኪዳን ጊዜ በእግዚአብሔር ስም ዙሪያ የነበረ የቅድስናን ግንዛቤ መመልከት ያስፈልጋል። በኦሪት ዘጸአት መጽሐፍ ውስጥ እንደሚነበብ፣ በሲና ተራራ ላይ ራሱን በገለጸበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር ህዝቡን ከግብጻዊያን ቀንበር ነፃ እንዲያወጣ ሙሴን አዘዘ። በዚህ ታላቅ ትእዛዝ ፊት፣ ሙሴ ብዙ ጥያቄ ያቀርባል፥ ሕዝቡን እንዴት ያሳምናል? የእግዚአብሔር ስም ማን ነው? “እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው፥ ‘እኔ ያለሁና የምኖር ነኝ’፤ ስለዚህም ‘እኔ ነኝ ወደ እናንተ ልኮኛል’ በላቸው” (አሪት ዘጸአት 3፥14)። ትምህርተ ክርስቶስ እንደሚያስተምረው፣ ይህ ስም “እግዚአብሔር የሕላዊና…
16Aprፋሲካ፥ የነገሮችን ይዘት ለመገምገም እንማር (EASTER: seeing the essence of things)
የእግዚአብሔር ህግ ፍጹምነት በአሮጌው እና በአዲሱ መካከል ባለው አስደናቂ አንድነት ይገለጻል። በዘላለማዊ አምላክ ጥበበኛ እጅ (ማለትም በመንፈስ ቅዱስ) የሚደረግ ሁሉ በዋጋ የማይተመን ስፌት ይመስላል። ✓ ፋሲካ የሚለ ቃል ከዕብራይስጥ ‘ፐሳህ’ ከሚል ቃል የመጣ ነው። ትርጉሙም ‘ሽግግር’ ማለት ነው። ስለሆነም፥ ሁለቱም ክስተቶች በሽግግር ተለይተው ይታወቃሉ፥ 1. የአይሁድ ፋሲካ፣ ከአራት መቶ ዓመታት ስደት በኋላ ከግብጽ ባርነት ወደ ስጋዊ ነፃነት በሙሴ አማካይነት ተፈጽሞአል። 2. የክርስትና ፋሲካ፣ ከአዳም ኃጢአት በኋላ ከሰይጣን ባርነት ወደ መንፈሳዊ ነፃነት በክርስቶስ መሥዋዕት አማካይነት ተፈጽሞአል። ክርስቶስ የሰማይን በር ስለከፈተልን፥ እንደየትጋታችን ቢሆንም ወደ መጀመርያው ገነት መመለስ እንችላለን። ✓ አሁን የሁለቱን ተመሳሳይነት እንመልከት። የአይሁድ ሕግ በአይሁድ ፋሲካ ወይም በቂጣ በዓል ቀን ለመስዋእት ከቀረበ በግ ጋር፣ እርሾ ያልገባበት ቂጣ እና መራራ እፅዋት እንዲበላ ያዝዛል፥ 1. በግ የንጽህናና የየዋህነት ምልክት ነው፣ በዚህ ምክንያት በግ…
10Apr[UR5] ኮቪድ-19 እና የእግዚአብሔር ቅጣት (1)
ኮቪድ-19 ስለእግዚአብሔር ቅጣት እንደገና እንድናስብ እያደረገ ነው፥ ነገር ግን ከቅዱሳት መጻሕፍት ጀምሮ ጉዳዩ ውስብስብ ነው። እግዚአብሔር ይቀጣልን? ለመረዳት እንሞክር። የመጀመሪያው መልስ በ2ኛ ጴጥሮስ 2፥4-17 ላይ እናገኛለን፥ “መላእክትን እንኳ ኃጢአት በሠሩ ጊዜ እግዚአብሔር ሳይራራላቸው በጨለመ ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ሆነው የፍርድን ቀን እንዲጠባበቁ ወደ ገሃነም ጣላቸው፥ እንዲሁም የጽድቅ ሰባኪ የነበረውን ኖኅን ከሌሎች ሰባት ሰዎች ጋር አድኖ እግዚአብሔርን የማያመልኩ ሰዎች በነበሩበት አለም ላይ የጥፋትን ውኃ ሲያመጣ ራርቶ የቀደመውም ዓለም አልማረውም፤ ደግሞ እግዚአብሔርን ለማያመልኩ ሁሉ የመቀጣጫ ምሳሌ እንዲሆኑ የሰዶምንና ገሞራን ከተሞች ዐመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጥሎ እንዲጠፉ ፈረደባቸው… ጻድቅ ሎጥም በመካከላቸው ሲኖር በየቀኑ ያየውና ይሰማው በነበረው ሕገ ወጥ ድርጊታቸው ጻድቅ ነፍሱ ትጨነቅ ነበር… ጌታ እግዚአብሔር እርሱን በማምለክ የሚኖሩትን ሰዎች ከፈተና እንደሚያድናቸው፥ ኃጢአተኞችንም እንዴት እንደሚቀጣና ለፍርድ ቀንም እንዴት ጠብቆ እንደሚያቆያቸው ያውቃል ማለት ነው… እነዚህ ግን ለመጠመድና…
03Aprየአብይ ጾም 5ኛ እሁድ (A LENT-5)
ወንገል፥ ዮሐንስ 11፥1-45 ቁ3 “ጌታ ሆይ፥ እነሆ ወዳጅህ ታሞአል”፥ … “ብዙዎች የእግዚአብሔር ወዳጆች በመጥፎ ነገር ሲሰቃዩ ማየት ያናድዳቸዋል። ለምሳሌ፣ የታመሙ ወይም ድሃ የሆኑ ወይም ሌሎች አሳዛኝ ሁኔታዎችን የተቋቋሙ አሉ። በዚህ ምክንያት የሚሰናከሉት የእግዚአብሔር ልዩ ወዳጅ እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች ለመቋቋም የእርሱ ድርሻ እንደሆነ አያውቁም። የአልዓዛርን ታሪክ ማየት እንችላለን፥ እርሱ የክርስቶስ ወዳጅ ነበረ ግን ታሞአል” (JOHN CHRYSOSTOM 344-407) “እዚህ ላይ ለወዳጅ የሚያስፈልገው አንድ ትእዛዝ ብቻ ነው፥ ነገር ግን ሴቶቹ ኢየሱስን ’ና’ ብለው አላዘዙም። ደግሞም ‘እዚያ እዘዝ እና እዚህ ይፈጸማል’ ለማለት አልደፈሩም። እነዚህ ሴቶች የተናገሩት ‘ጌታ ሆይ፥ እነሆ የምትወደው ታሞአል’ የሚል ቃል ብቻ ነው፤ ማለትም፥ አንተ ማወቅህ በቂ ነው፣ ምክንያቱም ሰውን ወደህ ለብቻ አትተውም” (AUGUSTINE 354-430) ቁ6 “እንደ ታመመም በሰማ ጊዜ ያን ጊዜ በነበረበት ስፍራ ሁለት ቀን ዋለ”፥ … “ለሞት ሙሉ በሙሉ ቦታ እንዴት እንደሰጠ ትመለከታለህ።…
28Marየአብይ ጾም 4ኛ እሁድ (A LENT-4)
ወንገል፥ ዮሐንስ 9፥1-41 ቁ7 “ሂድና በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ አለው”፥ … “እግዚአብሔርም ደግሞ ተናገረኝ እንዲህም አለኝ፥ ይህ ሕዝብ በጸጥታ የሚሄደውን የሰሊሆምን ምንጭ ውኃ ጠልቶአልና…” ብርቱና ብዙ ውኃ ባለው በኤፍራጥስ ወንዝ ተደስተዋል (ትንቢተ ኢሳይያስ 8፥5-7)። “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል” (መዝሙረ ዳዊት 23)። እምነት በጸጥታ በሚሄድ ውኃ ውስጥ፣ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይገኛል። እንቁም፣ ፀሎትን እንጨምር፣ ወደ ራሳችን እንግባ። እግዚአብሔር የሚገኘው በጸጥታ በሚፈስ ውሃ ውስጥ ነው እንጂ በኤፍራጥስ ወንዝ ብርቱ ግፊት ውስጥ አይገኝም። 1ኛ ንባብ፥ 1ኛ ሳሙኤል 16፥1-13 ሳሙኤል ዳዊትን ይቀባል፣ ከዚህ ቀን ጀምሮ ዳዊት ንጉሥ ነው። ነገር ግን ዳዊት እንደ ንጉሥ የሚገለጸው ከሳኦል ሞት በኋላ ብዙ ችግርና መከራ ካሸነፈ በኋላ ብቻ ነው። ሆኖም ግን ከዚያ በፊት እግዚአብሔር አስቀድሞ በስውር መርጦት ነበረ። ማንም እንደማያስተውለው እግዚአብሔር በስውር ይሠራል።…
20Marየአብይ ጾም 3ኛ እሁድ (A LENT-3)
ወንገል፥ ዮሐንስ 4፥5-42 ቁ6 “በዚያም የያዕቆብ የውሃ ጕድጓድ ነበረ። ኢየሱስም መንገድ ከመሄድ የተነሳ ስለደከመው በጕድጓድ አጠገብ ተቀመጠ፤ ጊዜውም ስድስት ሰዓት ገደማ ነበረ”፥ … እዚህ ላይ ሁለት ነገሮች ይጠቁማሉ፥ ድካምና ስድስተኛ ሰዓት። ስድስተኛ ሰዓት ክርስቶስ የተሰቀለበት ሰዓት ነው፣ ድካም ደግሞ የመስቀሉ ድካም ነው። በሰማርያ ጕድጓድና በመስቀል ላይ የተከሰተውን ማነጻጸር እንችላለን፥ በሰማርያ ጕድጓድ ኢየሱስ ውሃን ይጠይቃል፣ በመስቀል ላይ “ጠማኝ” ይላል። በሰማርያ ጕድጓድ ኢየሱስ የውሃን ጥማት ለዘላለም የሚያረካ የሕይወትን ውሃ ይሰጣል፣ በመስቀል ላይ ጎኑ ራሱ የሕይወት ውሃ ምንጭ ይሆናል። “ለሁሉ ሰው የሕይወት እስትንፋስ ምንጭ የሆነው ክርስቶስ በጉዞ ምክንያት ደክሞ ስለነበረ በሰማርያ የውሃ ምንጭ አጠገብ ተቀመጠ። ጊዜውም የሚያቃጥል ሙቀት ውቅት ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ጊዜው ስድስት ሰዓት ገደማ ነበረ። መሲሑ በጨለማ ያሉትን ሊያበራላቸው የመጣው እኩለ ቀን ነበር። ውሃን የፈጠረ ለመጠጣት ሳይሆን ለማንጻት ወደምንጩ መጣ። የዘላለማዊነት…
13Marየአብይ ጾም 2ኛ እሁድ (A LENT-2)
ወንገል፥ ማቴዎስ 17፥1-9 ቁ1 “ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው”፥ … “ከስድስት ቀንም በኋላ”፥ … ከባርነት ነፃ ወጥቶ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት ለመድረስ እስከ ዛሬ ድረስ አብሮ በምጥ ጭንቀት ተይዞ በመቃተት ላይ ያለው የፍጥረት ፍጻሜ ሰባተኛው ቀን (ሮሜ 8፥21-22) የሁሉ ፍጥረት አላማ ነው። “ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ”፥ … “ጴጥሮስ ያዕቆብና ዮሐንስ ከርሱ ጋር ባላቸው ቅርበትና ፍቅር ምክንያት ኢየሱስን ወደ ተራራ ይሸኛሉ” (JOHN CHRYSOSTOM 344-407) ታቦርና ደብረዘይት ማነፃፀር እንችላለን። በታቦር ላይ አብ ልጁን ሲጠራ፣ በደብረዘይት ላይ ኢየሱስ አባቱን ይጠራል። ታቦር ላይ ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ያሳያል፣ በደብረዘይት ደግሞ ኢየሱስ ሰው መሆኑን ያሳያል። ቁ2 “በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ”፥ … ይህ መለወጥ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሁሉ ያቀደ…
05Marየአብይ ጾም 1ኛ እሁድ (A LENT-1)
ወንገል፥ ማቴዎስ 4፥1-11 የኢየሱስ ፈተናዎች ከሦስት ጣዖታት ጋር የተዛመዱ ናቸው፥ እነሱም ድንጋዮችን ወደ እንጀራ የሚቀይር የኢኮኖሚ ጣዖት አምልኮ፤ እግዚአብሔርን መግዛት የሚፈልግ የሃይማኖት ጣዖት አምልኮና ሁሉን ሰው መግዛት የሚፈልግ የፖለቲካ ጣዖት አምልኮ ናቸው። ቁ1 “ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው”፥ … “ይፈተን ዘንድ”፥ … “ልጄ ሆይ፣ እግዚአብሔርን ለማገልገል ራስህን ካቀረብህ ለፈተና ተዘጋጅ” (ሲራክ 2፥1)። ጥሩ ውሳኔ ከተወሰነ በኋላ የመፅናት ትግል አለ። በግሪክ ቋንቋ “ፈተና” “peiro” ይባላል፣ “peiro” ማለት ማቋረጥ ማለት ነው፥ experience በማድረግ (experience = “peiro”), expert (“peiro”) እንሆናለን። በድሮ ታሪክ ፈተናዎች እንዲሁ ትምህርት ይባሉ ነበር፥ እሱም ልጆች መሆናችንን እንጂ ዳቃሎላዎች አለመሆናችንን የሚያረጋግጠው የልጅ ሕይወት ሥልጠና ነው (ዕብራውያን 12፥8) ፣ በእምነት ደረጃ የመጣራት ሥልጠና ነው (ያቆብ 1፥2-4፣ 1ጴጥሮስ 1፥6)። “ከዲያብሎስ”፥ … በግሪክ ቋንቋ “ዲያብሎስ” ማለት የሚከፋፍል ማለት…
06Feb[UR4] የቤኔዲክት ፲፮ አወጣት አሁንም ክፍት ነው (2) The withdrawal of Ratzinger is still open
በአሁኑ ጊዜ በቤተክርስቲያን ውስጥ በሁሉም ደረጃ ውስጥ አለመግባባትና መከፋፈል መኖሩ የማይካድ ሐቄ ነው። ታዲያ ይህን የተቋጠረ ነገር እንዴት ልንፈታው እንችላለን? እንደኔ አስተያየት ሁለት መንገዶች አሉ፣ አንዱ ለወደፊት የሚፈታ ሲሆን ሌላው ግን ለአሁን የሚሆን ነው። ሁለቱም ግን የሚቃረኑ ሳይሆኑ፣ እንዲያውም እርስ በራስ የሚደጋገፉ ናቸው። የመጀመሪያው መንገድ ቤኔዲክት ፲፮ በ2013 ለመልቀቅ ስለገፋፋቸው ምክንያቶች ጠለቅ ያለና ሚዛናዊ ጥናት ማካሄድ ነው፥ በእርግጥ የርሳቸውን ውሳኔ ሕገወጥ ማድረግ የሚችሉ ጫናዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ከሆነ፣ የፍራንሲስ መላው ጵጵስና ወዲያውኑ ሕገወጥ ይሆናል። ነገር ግን እንዲህ ዓይነት ጥናት ለማካሄድ፣ ሁለቱም የዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ ፈፃሚዎች መጀመሪያ መሞት አለባቸው (ይህ ደግሞ ለማንም መመኘት የማንፈልግ ነገር ነው)። ሁለተኛው መንገድ ቤኔዲክት ፲፮ ከስልጣን ለመልቀቅ ያቀዱትን አዲስ አፈፃፀም ጠለቅ ያለና የስውን ክብር የሚጠብቅ ትንታኔ ማድረግ ነው፥ ይህ ደግሞ አሁንም በፍጥነት ሊከናወን ይችላል። በቅዱስ ጴጥሮስ…
06Feb[UR3] የቤኔዲክት ፲፮ አወጣጥ አሁንም ክፍት ነው (1) The withdrawal of Ratzinger is still open
የሐዋርያ ጴጥሮስ መሪነት ክርስቶስ በተናገረው ቃላት ላይ ተመሰረተ፥ “እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም” (ማቴዎስ 16፥18)። ነገር ግን የዛሬ የካቶሊክ መሪዎች ካቶሊካዊ እምነትን በተደጋጋሚ እየደበደቡ ነው። እግዚአብሔር ክልስ እንደነበረ ተብሎአል፣ ማርያም ተራ ልጅ እንደነበረች ተብሎአል (እናስ ያለ ሐጢያት የተፀነሰች አልነበረችምን?) ወይስ በእግዚአብሔር ላይ እንደተናደደች ተብሎአል (የፍጡራን ለእምነትና ለታዛዥነት ምሳሌ አይደለችምን?)። ከዚህ በፊት በሰው መሥዋዕት ብቻ የምትረጋጋ ፓቻማማ የምትባል ህይወት የሌላትና የደረቀች የደቡብ አሜሪካ ጣኦት ከማርያም ጋር በተመሳሳይ ደረጃ ላይ ማስቀመጥ ተችሎአል። ለዚህ ሁሉ ok ተባለ። የክርስቶስ ወንጌል የጋብቻን ፍቺ ያልፈቀደ ምህረትን በመርሳት እንደሆነ፣ ሆኖም በክርስቶስ ጊዜ የድምጽ መቅረጫዎች ስላልነበሩ የወንጌልን ቃላት በትክክል ማወቅ እንደማንችለው ማለት ትችሎአል። ድርብ ok ተባለ። ሶዶም ከተማ የተቃጠለችው በግብረ ሰዶማዊነት ምክንያት ሳይሆን እንግዳን ባለመቀበል ምክንያት በማለት፣ ብሉይ ኪዳን…

መግቢያ - Entrance
1 ነገሥት 17፡2-7 ያንብቡ፥ የእስራኤል ሕዝብ የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት ስላልፈለገ፣ እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያሰን ወደ በረሀ ሄዶ በምስጥራዊ ቦታ እንዲሸሸግ ነገረው። በዚህ ምክንያት ሁለት ተቃራኒ ሁኔታዎችን ማነፃፀር እንችላለን፥ በአንድ በኩል የእግዚአብሔርን ድምጽ ያጣው ሕዝብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ በከሪት ሽለቆ ከእግዚአብሔር ቀጥተኛ መመሪያ እና ምግብ የሚቀበል ነቢይ። ስለዚህ የእግዚአብሔር ድምፅ አሁንም ድረስ ወደሚሰማበት ምስጥራዊ ሸለቆ እንግባ።

የታችኛው ክፍል - Lower Room
በዚህ ክፍል ውስጥ ከማህበራዊ ጉዳይና ከዓለም አቀፍ መስተዳደር ጉዳዮች ጀምሬ በመጽሐፍ ቅዱስ እና በጥንታዊ የክርስቲያን ትምህርት በመሞርክስ፣ አንዳንድ ወሳኝ ግንዛቤዎች አቀርብላችኋለሁ። የሐዋርያውን ጳውሎስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ያንብቡ፥ “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ” (ወደ ሮሜ ሰዎች - ምዕራፍ 12፡2)።

የላይኛው ክፍል - Upper Room
አሁን ባለን ታሪክ ውስጥ ጣዕሙን እንዳጣ ጨው ሆነው የተወሰኑ ክርስቲያን አማኞች እና በተለይ መሪዎች የዚህን ዓለም አካሄድ ለመከተል ከፍተኛ ጉጉት ያድርባቸዋል። ለሰርዴስ መልአክ የተሰጠውን ምክር ያስታውሱ፥ “የነቃህ ሁን፣ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና” (የዮሐንስ ራእይ - ምዕራፍ 3፡2)። ክርስቶስ ቀርቦአል፣ ሲመጣም ከጓደኞቹ ቁጥር መገኘት እንፈልጋለን።

የውኃ ጉድጓድ - Water Well
ከጊዜ ወደ ጊዜ ፈጽሞ በማይደርቁ ጥንታዊ ምንጮች አጠገብ አርፌ ማታደስን አገኛለሁ። “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?” (መዝሙረ ዳዊት - ምዕራፍ 42)። ቀጣዮቹ ገጾች ክርስቶስን ለመማረክ ማንኛውንም ነገር ለመተው ከመረጡ ከዛሬና ትላንት አማኞች ልብ ይወጣሉ።

እንጀራ ቤት - Kitchen
እና እዚህ ደረስን። የክርስቶስ ወዳጅ ከምድራዊ ደስታ አይገለልም። “እግዚአብሔር ሥራህን ተቀብሎታልና ሂድ፥ እንጀራህን በደስታ ብላ፥ የወይን ጠጅህንም በተድላ ጠጣ” (መጽሐፈ መክብብ - ምዕራፍ 9፡7)። በእግዚአብሔር እይታ መሠረት የሚኖሩት ሰዎች የዝናን የወይን ጠጅ ይጠጣሉ፣ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ይሰማቸዋል።