- 13Dec
የሰብከተገና 1ኛ እሁድ (A ADV-1)
ወንገል፥ ማቴዎስ 24፥37-44 ቁ37-39 “የኖኅ ዘመን እንደ ነበረ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና። በዚያን ዘመን ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም ነበረ፥ የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከ ወሰደ ድረስ እንዳላወቁ፥ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል”፥ … በአጭር ቃላት ጌታችን ሰዎች በመንፈሳዊ ነገሮች ፊት ያላቸውን የግድየለሽነት ሁኔታ ያብራራል። መብላትና መጠጣት፣ ሚስት ወይም ባል ማግባት ይበልጥ አስፈላጊ እንደሆነ ተደርጎ ይቆጠራል። በዚህ መንገድ ሲኖሩ ግን ሰዎች ከሁሉ የሚበልጥ ነገር የዘላለም ሕይወት መሆኑን ይረሳሉ። ሰዎች ጥሩ ቢሆንም መጥፎ በንግዳቸው ላይ እያሉ፣ ሁለተኛ የሰው ልጅ መምጣት ባልተጠበቀ ሰዓት ይፈጸማል። “የክርስቶስ ተቃዋሚ ሲመጣ፣ ራሳቸውን ማዳን ተስፋ መቁረጥን ከለመዱ አመጸኞች መካከል፣ ሕገወጥ ደስታን መፈጸም በጉጉት ይጠብቃሉ። ሆዳምነት መናፈቅና ስካር ይኖራል” (CHRYSOSTOM) “በመርከቧ ውስጥ ካመለጡት በስተቀር የምድር ፍጥረታት ሁሉ በጥፋት ውኃ…
08Decያለ ኃጢአት የተፀነሰች ማርያም (Immaculate Conception)
“ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፣ የአገሬ ልጅ፣ የነፍሴ እህት፣ የደስታዬ ደስታ ደስ ይበልሽ። እኔ በሌሊት እንደሚጓዝ ነኝ፣ አንቺ ግን ከጠፈር በታች መጠለያ ነሽ። እኔ የተጠማ ጽዋ ነኝ፣ አንቺ ግን የእግዚአብሔር ክፍት ባህር ነሽ። ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፣ የአገሬ ክንፍ፣ የነፍሴ አክሊል፣ የደስታዬ ደስታ ደስ ይበልሽ። የተባረክሽ ነሽ የሚሉሽ ሁሉ ደስ ይበላቸው” (Gertrud Von le Fort)
06Decየሦስታኛ አመት 34ኛ እሁድ (C OT-34) ክርስቶስ ንጉሥ
ወንገል፥ ሉቃስ 23፥35-43 የዚህ እሁድ ንባብ የመዳን መርህ የሆነውን የኢየሱስን ንግሥና ይገልጽልናል። ኢየሱስ ንጉሥ ከመስቀል አናት ሆኖ በምን ዓይነት ሁኔታ ሊያድነን እንድሚችል እንረዳለን። እሱ የሚያገለግል ንጉሥ ነው፤ ያለው ስልጣን እስከ ሞት መውደድ ብቻ ነው። በመስቀል ላይ፣ ኢየሱስ መንግሥቱን ይፈጽማል፣ እሱ ንጉስ ነው። ድሃ፣ የተራበ፣ የሚያለቅስ፣ የተጠላ፣ የተሰደደ፣ የተሰደበና ተቀባይነት ያላገኘ፣ ጠላቶቹን የሚወድና የሚባርካቸው፣ ክፉን በመሸከም ክፉን የሚያሸንፍ ነው። ቁ35 “ሕዝቡ ቆሞ ይመለከት ነበር”፥ … ስለስቅለቱ ማሰላሰል የአዲሱ ጥበብ መርህ ነው። በጎልጎታ ላይ የፊቱ መጋረጃ ስለሚነሳ ክርስቶስን ልንመለከተው እንችላለን፥ እርሱ ገደብ የሌለው ፍቅር ነው። ቁ36 “ሆምጣጤ ሰጡት”፥ … “በምግቤ ውስጥ ሐሞት ቀላቀሉ” (መዝሙር 69፥21)። ጥማቱ የሕይወትን ውሃ እንዲሰጠን ነው። እኛ ደግሞ በምላሹ ሞታችንን እንሰጠዋለን። ቁ38 “ይህ የአይሁድ ንጉሥ ነው”፥ … ጲላጦስ “ይህ የአይሁድ ንጉሥ ነው” በመጻፍ የፍርዱ ምክንያት መግለጽ ፍለጎ ነበረ (ማርቆስ…
30Novየሦስታኛ አመት 33ኛ እሁድ (C OT-33)
ወንገል፥ ሉቃስ 21፥5-19 ቁ5 “አንዳንድ ሰዎች “ይህ ቤተመቅደስ እንዴት ውብ ነው፣ በከበሩ ድንጋዮችና ለእግዚአብሔር በቀረቡ ስጦታዎች አጊጦአል” እያሉ ይነጋገሩ ነበር”፥ … ሄሮድስ በአስር ዓመታት ውስጥ በ 100,000 ሠራተኞችና ቅድስተ ቅዱሳንን ለመስራት እንደ ጠራቢ በሰለጠኑት 1,000 ካህናት ተጠቅሞ የገነባው እጅግ አስደናቂ ቤተመቅደስ ነው። በ 20 ዓ.አ የተጀመረው ሥራ ለረጅም ጊዜ ቀጥሎአል፥ ከመፍረሱ ስድስት ዓመት በፊት በ 64 ዓ.ም ውስጥ ያበቃል። “በከበሩ ድንጋዮች”፥ በነጭ የኖራ ውብ ድንጋይ ከተሠራ ከጥንታዊው ቤተመቅደስ ምንም አያንስም፥ የክርስቶስ አካል በመስቀል ላይ እንደሚጠፋ ቤተመቅደስም ይፈርሳል። የአዲሱ ቤተመቅደስ የማዕዘን ድንጋይ የተሰቀለ ክርስቶስ ነው። ወደ ጌታችን ቀርበው እንደ ህያው ድንጋይ ደቀመዛሙርቱ ለአዲሱ መንፈሳዊ ቤተመቅደስ ግንባታ ተቀጥረዋል (1ኛ ጴጥሮስ 2፥4)። ቁ8 ደቀመዛምርቱ ኢየሩሳሌም እንደምትጠፋ በሰሙ ጊዜ ይህንን ክስተት የሚያውጅ ምልክት የትኛው እንደሆነ ይጠይቁታል። ኢየሱስ በማስጠንቀቅ ይመልስላቸዋል፥ “እንዳትሳሳቱ ተጠንቀቁ” ምንም ማስጠንቀቂያ አትጠብቁ፣ ሐሰተኛ ነብያት እንዳያታልሉአችሁ…
22Novእናንተም ደግሞ መሄድ ትፈልጋላችሁ? (ዮሐ 6፥68)
1. አንዳንድ ክርስቲያኖች በመጽሐፍ ቅዱስ ሁለት የተለያዩ አማልክት አሉ ብለው በማወቅ ወይም ባለማወቅ ያምናሉ። ሁለተኛው አምላክ የመጀመሪያው አምላክ “ዝግመተ ለውጥ” ነው ብለው ያምናሉ። አንዱ ህጉን የሚያስገድድ ብርቱው ፈራጅ የሆነው የብሉይ ኪዳን አምላክ ሲሆን፣ አንዱ ደግሞ የአዲስ ኪዳን አምላክ ነው። ሁለቱም ከምህረትና ይቅር ባይነት አንፃር እርስ በርሳቸው የሚቃረኑ ናቸው። እስከዚህ ያብራራሁት “ግኖሲስ” ተብሎ የሚጠራ በክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያው መናፍቅ ነው (በእንግልዝኛ Gnosis ወይም Gnosticism)። የመጀመርያ ክርስቲያን ግኖሲስ ኢየሱስን እንደ “አዲስ ሰይጣን” አድርጎ ያስበው ነበር። ምንም እንኳ የማይረዳ ቢመስልም፣ በግኖሲስ ትምህርት መሰረት፣ በክፉ ፈጣሪ (የብሉይ ኪዳን አምላክ) ለተፈጠረ ለአዳም ዕውቀትና ነፃነት በማሳየት (“ግኖሲስ” በግሪክ ቋንቋ “እውቀት” መለት ነው)፣ ሰይጣን የብርሃን ምንጭ ነው ይለዋል። እንደ ግኖሲስ አስተሳሰብ፣ ዓለም በክፉ አምላክ የተፈጠረች የሰው ዘር የታሰረባት እስር ቤት ናት ብሎ ያምናል። ስለዚህ የፈጣሪ አምላክ ሕግ የሰው…
16Novየሦስታኛ አመት 31ኛ እሁድ (C OT-31)
ወንገል፥ ሉቃስ 19፥1-10 ቁ1 “ኢየሱስ ወደ ኢያሪኮም ከተማ ገብቶ ያልፍ ነበር”፥ … ቀደም ባለው ምዕራፍ (ሉቃስ 18) ኢየሱስ ወደ ኢያሪኮ ቀርቦ ዓይነሰውሩን ፈውሷል። አሁን ገብቶ ከተማውን እንደ አሸናፊ ሆኖ ያቋርጣታል። ሊደፈር የማይችል የኢያሪኮ ምሽግ ፈርሶአል። ዐይን ተፈወሰ፣ ብርሃንም ወደ ልብ የሚገባ ሲሆን ድንዛዜውን ይቀልጣል። የሰው ጨለማ ተቀደደ። ቁ2-4 “እነሆም ዘኬዎስ የሚባል ሰው፥ እርሱም የቀራጮች አለቃ ነበረ፥ ባለ ጠጋም ነበረ። ኢየሱስንም የትኛው እንደ ሆነ ሊያይ ይፈልግ ነበር፤ ነገር ግን ቁመቱ አጭር በመሆኑ ከሕዝብ ብዛት የተነሳ አቃተው። ኢየሱስ በዚያ በኩል ያልፍ ስለነበር ዘከወዎስ ያየው ዘንድ ወደ ፊት በመሮጥ በአንድ ሾላ ዛፍ ላይ ወጣ”፥ … ሰዎቹ መንገድ ውስጥ ስለገቡ ኢየሱስ እንዳይታይ ዘኬዎስን ከልክለውት ነበር። ዘኬዎስ ግን ሕዝቡን ችላ በማለት “ሞኝ ፍሬ” የሚያፈራ የሾላ ዛፍ ላይ ወጣ። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደተናገረው፥ “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም…
01Novየሦስተኛ አመት 29ኛ እሁድ (C OT-29)
ወንገል፥ ሉቃስ 18፥1-8 see here ቁ3 “በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች”፥ ሙሽራው ተወስዶባት መቼ እንደሚመለስ የማታውቅ መበለት የሉቃስ ቤተክርስቲያን ናት ”(5፥35፤ ሐዋ 1፥9-11)። መመለሻውን በመመኘት ብቻዋንና በሐዘን የምትኖር ናት። ለዚህም “ማራናታ” (1ቆሮ 16፥22፤ ራዕ 22፥20) ብላ ትለምናለች። መበለቲቱ ምንም ስጦታ የላትም። እንደ ሰው ምኞት ድሀ ናት። ፍላጎቷን ማሟላት የምትችለው አጥብቆ በመጠየቅ ብቻ ነው። 1ኛ ንባብ ዘጸአት 17፥8-13 see here ቁ8 “አማሌቅም መጥቶ ከእስራኤል ጋር በራፊድም ተዋጋ”፥ አማሌክ ወደ ቅድስት ምድር የሚመራውን መንገድ ይክዳል። ሙሴ እጆቹን በክርስቶስ መስቀል መልክ በመዘርጋት ይከፍተዋል። (AUGUSTINE) ቁ12 “የሙሴ እጆች ግን ከብደው ነበር፤ ድንጋይም ወሰዱ፥ በበታቹም አኖሩ፥ እርሱም ተቀመጠበት፤ አሮንና ሖርም አንዱ በዚህ አንዱ በዚያ ሆነው እጆቹን ይደግፉ ነበር፤ ፀሐይም እስክትገባ ድረስ እጆቹ ጠነከሩ”፥ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ግን በገዛ ኃይሉ በመስቀል ላይ እጆቹን ወደ ላይ ዘረጋ። ምስል እንዴት እንደተሰጠና እውነት እንዴት እንደሆነ…
26Octየሦስተኛ አመት 28ኛ እሁድ (C OT 28)
ወንገል፥ ሊቃስ 17፥11–19 see here ቁ14 “እነርሱም በመሄድ ላይ ሳሉ ከለምጻቸው ነጹ”፥ እኛ ቅዱስ ጉዞውን ለሚመራን ለቃሉ በመታዘዝ እንነጻለን። ቁ15 “ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ ተመለሰ”፥ ይህ “አንድ ብቻ” የእውነተኛው እስራኤል የቤተክርስቲያን ምስል ነው። ቁ17-18 “አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ? ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም?”፥ አንድ እና ዘጠኝ እናነፃፅር። ብዛትን በተመለከተ ዘጠኝ ከአንድ ይበልጣል፥ ዘጠኝ ለማግኘት ዘጠኝ ጊዜ አንድ ያስፈልጋል። ነገር ግን ጥራትን በተመለከተ አንድ ቁጥር ከዘጠኝ ቁጥር ይበልጣል፥ አንድ ቁጥር የሙላት ስሜት ይሰጣል። ዘጠኝ ቁጥር ግን፣ አሥር ለመሞላት አንድ ስለሚጎድለው፣ የእጥረት አምሳያ ነው። አንድ ሲባል ከሌላ ሁሉ የተለየ ነው። እግዚአብሔር ከነፍስ ወደ ነፍስ ለያንዳንዱ ልብ ይናገራል። የክርስቶስ ፀጋ በእያንዳንዱ ሰው ነፍስ ውስጥ ይከሰታል እንጂ ለዘጠኝ ወይም ለአሥር ወይም ለጋራ አይከሰትም። ይህ ማለት በክርስትና ሕይወት ውስጥ ዋጋ ያለው…
17Octስለአየር ንብረት ያለው ክርክር የፖለቲካ መሣሪያ ነው
የሙቀት መጠን። በአሜሪካ ውስጥ በሙቀት መጠን ላይ ያሉትን መረጃዎች ከተመለከትን፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በእውነት የሙቀት መጠን ያደገ ይመስላል፣ ግን ከዚህ በታች ያለው ግራፍ እንደሚያሳየው፣ መረጃዎችን በረጅም እይታ ውስጥ ማየት ያስፈልጋል፤ የሁለት ክፍለዘመን ጊዜ ጥናት ውስጥ የምናስገባ ከሆነ፣ በሙቀት መጠን ላይ ያሉት መረጃዎች አይያሳስቡንም። የሰው ስራና የሙቀት መጠን። ከ 1940 እስከ 1975 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ የኢንዱስትሪ ከፍተኛ እድገት እየታየ፣ ዓለም አቀፍ የሙቀት መጠን ዝቅ ያለበት ምክንያት ለምን ነው? ታሪክና የሙቀት መጠን። ያለፉት 1000 ዓመታት ከተመረመሩ፣ አለም አቀፍ የሙቀት መጠን ወደ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰው ከኢንዱስትሪ ዘመን በፊት ነው (በመካከለኛ ዘመን ላይ!)። ለምንድነው? CO2 የፀሐይ እንቅስቃሴእና የሙቀት መጠን። ከአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ከጀመርን፣ የሙቀት መጠን ከፀሐይ እንቅስቃሴ ጋር እንጂ ከCO2 እንቅስቃሴ ጋር አይሄድም። ለምንድነው? እንቁላል ወይስ ዶሮ ይቀድማል?። ሙቀት ወይስ የCO2 ልቀት ይቀድማል?…
10Octየአማዞን የጳጳሳት ጉባኤ (ሲኖዶስ)
ባለፈወ ጥቅምት 4 በቫቲካን ጋርደን በአማዞን ሲኖዶስ መክፈቻ ስነ-ሥርዓት ላይ የሆነውን ነገር አስተውላችኋል? ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ አረማዊ ንጥረ ነገሮችን ያካተተ ሥነ ሥርዓት ላይ ተሳትፈዋል። የተለያዩ የአማዞን ሕዝብ መሪዎች ለእናት ምድር ጸሎት አቀረቡ። አንድ ዛፍ ተተክሎአል። አንድ ሰው በጉልበቱ ተንበርክኮ የቆሻሻ አቧራ ስሞአል። ከዝግጅቱ በኋላ ተሳታፊዎች ነፍሰጡር ሴቶች እና እናት ምድር የሚመስሉትን ሐውልቶች በግንባራቸው መሬት ላይ ተደፍተው ሲሰግዱ ታይተዋል። የእግዚአብሔር ቃልና የቤተክርስቲያን ትምህርትና ምስጥራት እስካሉ ድረስ፣ ወንጌልን መስበክ ይቻላል። ነገር ግን ወንጌላዊ ተልእኮ በአረማውያን ሥነ-አምልኮ ውስጥ መሳተፍን ያካትታል ብሎ የሚያስተምር መመሪያ አላውቅም። ከአረማውያን ጋር መነጋገር አለብን ከሚሉ ሰዎች ጋር መሄድ አያስፈልግም። ሚሽነሪዎች በአማዞን አካባቢ ገብተው እግዚአብሔር ዓለምን ስለወደደ አንድ ልጁን አሳልፎ እንደሰጠ ከልብና በፍቅር እንዲናገሩ ይገባል። የቤተክርስቲያን ተውፊት ክርስቶስን እንድንሰብክ ያስተምረናል። ይሁን እንጂ ከአረማውያን ጋር እንድንወያይ፣ በአረማውያን አምልኮ ውስጥ እንድንሳተፍም…

መግቢያ - Entrance
1 ነገሥት 17፡2-7 ያንብቡ፥ የእስራኤል ሕዝብ የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት ስላልፈለገ፣ እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያሰን ወደ በረሀ ሄዶ በምስጥራዊ ቦታ እንዲሸሸግ ነገረው። በዚህ ምክንያት ሁለት ተቃራኒ ሁኔታዎችን ማነፃፀር እንችላለን፥ በአንድ በኩል የእግዚአብሔርን ድምጽ ያጣው ሕዝብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ በከሪት ሽለቆ ከእግዚአብሔር ቀጥተኛ መመሪያ እና ምግብ የሚቀበል ነቢይ። ስለዚህ የእግዚአብሔር ድምፅ አሁንም ድረስ ወደሚሰማበት ምስጥራዊ ሸለቆ እንግባ።

የታችኛው ክፍል - Lower Room
በዚህ ክፍል ውስጥ ከማህበራዊ ጉዳይና ከዓለም አቀፍ መስተዳደር ጉዳዮች ጀምሬ በመጽሐፍ ቅዱስ እና በጥንታዊ የክርስቲያን ትምህርት በመሞርክስ፣ አንዳንድ ወሳኝ ግንዛቤዎች አቀርብላችኋለሁ። የሐዋርያውን ጳውሎስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ያንብቡ፥ “የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ” (ወደ ሮሜ ሰዎች - ምዕራፍ 12፡2)።

የላይኛው ክፍል - Upper Room
አሁን ባለን ታሪክ ውስጥ ጣዕሙን እንዳጣ ጨው ሆነው የተወሰኑ ክርስቲያን አማኞች እና በተለይ መሪዎች የዚህን ዓለም አካሄድ ለመከተል ከፍተኛ ጉጉት ያድርባቸዋል። ለሰርዴስ መልአክ የተሰጠውን ምክር ያስታውሱ፥ “የነቃህ ሁን፣ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና” (የዮሐንስ ራእይ - ምዕራፍ 3፡2)። ክርስቶስ ቀርቦአል፣ ሲመጣም ከጓደኞቹ ቁጥር መገኘት እንፈልጋለን።

የውኃ ጉድጓድ - Water Well
ከጊዜ ወደ ጊዜ ፈጽሞ በማይደርቁ ጥንታዊ ምንጮች አጠገብ አርፌ ማታደስን አገኛለሁ። “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ፥ አቤቱ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፤ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?” (መዝሙረ ዳዊት - ምዕራፍ 42)። ቀጣዮቹ ገጾች ክርስቶስን ለመማረክ ማንኛውንም ነገር ለመተው ከመረጡ ከዛሬና ትላንት አማኞች ልብ ይወጣሉ።

እንጀራ ቤት - Kitchen
እና እዚህ ደረስን። የክርስቶስ ወዳጅ ከምድራዊ ደስታ አይገለልም። “እግዚአብሔር ሥራህን ተቀብሎታልና ሂድ፥ እንጀራህን በደስታ ብላ፥ የወይን ጠጅህንም በተድላ ጠጣ” (መጽሐፈ መክብብ - ምዕራፍ 9፡7)። በእግዚአብሔር እይታ መሠረት የሚኖሩት ሰዎች የዝናን የወይን ጠጅ ይጠጣሉ፣ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ይሰማቸዋል።