-
22Jan
[WW1] ምንም የማያጣ (ቅዱስ ባስልዮስና ግሮጎርዮስ) Who has nothing to lose (Saint Basil and Gregory Nazianzus)
ቅዱስ ባስልዮስና ቅዱሰ ግሮጎርዮስ “ክርስቶስ አምላክ አይደለም” በሚል በአርዮስ መናፍቅነት ጊዜ በሰሜናዊ ቱርክ ቀጰዶቅያ በሚባል ክልል ውስጥ ጳጳሳት ነበሩ። ስለ አርዮስ የሚገልፅ የኒቂያ ጉባኤ ግልጽ ማረጋገጫ ቢኖርም፣ መናፍቃን ተስፋ አልቆረጡም ነበረ። ባስልዮስና ግሮጎርዮስ መናፍቅነትን ለማጥፋት ባከናወኑት ትግል ውስጥ ለእውነት በመቆም የማይሸነፉ ሀይሎች ነበሩ። ራሱ የአርዮስ ተከታይ የነበረ ንጉሥ ዩልያኖስ ለመናፍቃን ቅዱስ ቁርባን እንዲፈቀድላቸው ጳጳሳትን ለማስገደድ በሞከረ ጊዜ፣ ባስልዮስና ግሮጎርዮስ ለመታዘዝ አልቻሉም። አንድ ቀን በባስልዮስና በክልሉ አስተዳዳሪ መካከል የተከሰተ ክርክር፣ በአሁኑ ጊዜ ያልተለመደ የአንድ ጳጳስ ጥንካሬና ምሳሌነት ያሳያል። የክልሉ አስተዳዳሪ፣ የባስልዮስ ተቃውሞ ሲያጋጥመው፥ “መላው ዓለም የሚሰግድለትን የንጉሠ ነገሥቱን ፈቃድ ለመቃወም እብዳችኋልን? የንጉሠ ነገሥቱን ቁጣ፣ ስደት ወይም ሞት አትፈሩምን?” ሲል፣ ባስልዮስ ረጋ ብሎ “ምንም ንብረት የሌለው ንብረትን ማጣት አያስፈራራውም፤ ምድር ሁሉ ቤቴ ስለሆነች ልታሳድዱኝ አትችሉም፤ ሞት እንኳን ቢሆን ለእኔ መስጠት ከምትችሉት ታላቅ…
0 comments Read more